መዝሙር 150

1 ሃሌ ሉያ። እግዚአብሔርን በመቅደሱ አመስግኑት፤ በኃይሉ ጠፈር አመስግኑት።

2 በችሎቱ አመስግኑት፤ በታላቅነቱ ብዛት አመስግኑት።

3 በመለከት ድምፅ አመስግኑት፤ በበገናና በመሰንቆ አመስግኑት።

4 በከበሮና በዘፈን አመስግኑት፤ በአውታርና በእምቢልታ አመስግኑት።

5 ድምፁ መልካም በሆነ ጸናጽል አመስግኑት፤ እልልታ ባለው ጸናጽል አመስግኑት።

6 እስትንፋስ ያለው ሁሉ እግዚአብሔርን ያመስግን። ሃሌ ሉያ።