ምዕራፍ 2።

1፤ የባቢሎንም ንጉሥ ናቡከደነፆር ወደ ባቢሎን ከማረካቸው ምርኮኞች ወደ ኢየሩሳሌምና ወደ ይሁዳ ወደ እየከተማቸው የተመለሱት የአገር ልጆች እነዚህ ናቸው።

2፤ ከዘሩባቤል፥ ከኢያሱ፥ ከነህምያ፥ ከሠራያ፥ ከረዕላያ፥ ከመርዶክዮስ፥ ከበላሳን፥ ከመሴፋር፥ ከበጉዋይ፥ ከሬሁም፥ ከበዓና ጋር መጡ።

3፤ የእስራኤልም ሕዝብ ሰዎች ቍጥር ይህ ነው፤ የፋሮስ ልጆች፥ ሁለት ሺህ መቶ ሰባ ሁለት።

4፤ የሰፋጥያስ ልጆች፥ ሦስት መቶ ሰባ ሁለት።

5፤ የኤራ ልጆች፥ ሰባት መቶ ሰባ አምስት።

6፤ ከኢያሱና ከኢዮአብ ልጆች የሆኑ የፈሐት ሞዓብ ልጆች፥ ሁለት ሺህ ስምንት መቶ አሥራ ሁለት።

7፤ የኤላም ልጆች፥ ሺህ ሁለት መቶ አምሳ አራት።

8፤ የዛቱዕ ልጆች፥ ዘጠኝ መቶ አርባ አምስት።

9፤ የዘካይ ልጆች ሰባት መቶ ስድሳ።

10፤ የባኒ ልጆች፥ ስድስት መቶ አርባ ሁለት።

11፤ የቤባይ ልጆች፥ ስድስት መቶ ሀያ ሦስት።

12፤ የዓዝጋድ ልጆች፥ ሺህ ሁለት መቶ ሀያ ሁለት።

13፤ የአዶኒቃም ልጆች፥ ስድስት መቶ ስድሳ ስድስት።

14፤ የበጉዋይ ልጆች፥ ሁለት ሺህ አምሳ ስድስት።

15፤ የዓዲን ልጆች፥ አራት መቶ አምሳ አራት።

16፤ ከሕዝቅያስ ወገን የአጤር ልጆች፥ ዘጠና ስምንት።

17፤ የቤሳይ ልጆች፥ ሦስት መቶ ሀያ ሦስት።

18፤ የዮራ ልጆች፥ መቶ አሥራ ሁለት።

19፤ የሐሱም ልጆች፥ ሁለት መቶ ሀያ ሦስት።

20፤21፤ የጋቤር ልጆች፥ ዘጠና አምስት። የቤተ ልሔም ልጆች፥ መቶ ሀያ ሦስት።

22፤ የነጦፋ ሰዎች፥ አምሳ ስድስት።

23፤ የዓናቶት ሰዎች፥ መቶ ሀያ ስምንት።

24፤ የዓዝሞት ልጆች፥ አርባ ሁለት።

25፤ የቂርያትይዓሪምና የከፊራ የብኤሮትም ልጆች፥ ሰባት መቶ አርባ ሦስት።

26፤ የራማና የጌባ ልጆች፥ ስድስት መቶ ሀያ አንድ።

27፤ የማክማስ ሰዎች፥ መቶ ሀያ ሁለት።

28፤ የቤቴልና የጋይ ሰዎች፥ ሁለት መቶ ሀያ ሦስት።

29፤ የናባው ልጆች፥ አምሳ ሁለት።

30፤ የመጌብስ ልጆች፥ መቶ አምሳ ስድስት።

31፤ የሁለተኛውም ኤላም ልጆች፥ ሺህ ሁለት መቶ አምሳ አራት።

32፤ የካሪም ልጆች፥ ሦስት መቶ ሀያ።

33፤ የሎድና የሐዲድ የኦኖም ልጆች፥ ሰባት መቶ ሀያ አምስት።

34፤ የኢያሪኮ ልጆች፥ ሦስት መቶ አርባ አምስት።

35፤ የሴናዓ ልጆች፥ ሦስት ሺህ ስድስት መቶ ሠላሳ።

36፤ ካህናቱ፤ ከኢያሱ ወገን የዮዳኤ ልጆች፥ ዘጠኝ መቶ ሰባ ሦስት።

37፤ የኢሜር ልጆች፥ ሺህ አምሳ ሁለት።

38፤ የፋስኮር ልጆች፥ ሺህ ሁለት መቶ አርባ ሰባት።

39፤ የካሪም ልጆች፥ ሺህ አሥራ ሰባት።

40፤ ሌዋውያኑ፤ ከሆዳይዋ ወገን የኢያሱና የቀድምኤል ልጆች፥ ሰባ አራት።

41፤ መዘምራኑ፤ የአሳፍ ልጆች፥ መቶ ሀያ ስምንት።

42፤ የበረኞች ልጆች፤ የሰሎም ልጆች፥ የአጤር ልጆች፥ የጤልሞን ልጆች፥ የዓቁብ ልጆች፥ የሐጢጣ ልጆች፥ የሶባይ ልጆች፥ ሁሉ መቶ ሠላሳ ዘጠኝ።

43፤ ናታኒም፤ የሲሐ ልጆች፥ የሐሡፋ ልጆች፥

44፤ የጠብዖት ልጆች፥ የኬራስ ልጆች፥ የሲዓ ልጆች፤

45፤ የፋዶን ልጆች፥ የልባና ልጆች፥

46፤ የአጋባ ልጆች፥ የዓቁብ ልጆች፥ የአጋብ ልጆች፥ የሰምላይ ልጆች፥ የሐናን ልጆች፥

47፤ የጌዴል ልጆች፥ የጋሐር ልጆች፥ የራያ ልጆች፥

48፤ የረአሶን ልጆች፥ የኔቆዳ ልጆች፥

49፤ የጋሴም ልጆች፥ የዖዛ ልጆች፥ የፋሴሐ ልጆች፥

50፤ የቤሳይ ልጆች፥ የአስና ልጆች፥ የምዑናውያን ልጆች፥ የንፉሰሲም ልጆች፥

51፤ የበቅቡቅ ልጆች፥ የሐቁፋ ልጆች፥ የሐርሑር ልጆች፥

52፤ የበስሎት ልጆች፥ የምሒዳ ልጆች፥

53፤ የሐርሳ ልጆች፥ የበርቆስ ልጆች፥

54፤ የሲሣራ ልጆች፥ የቴማ ልጆች፥ የንስያ ልጆች፥ የሐጢፋ ልጆች።

55፤ የሰሎሞንም ባሪያዎች ልጆች፤ የሶጣይ ልጆች፥ የሶፌሬት ልጆች፥ የፍሩዳ ልጆች፥

56፤ የየዕላ ልጆች፥ የደርቆን ልጆች፥ የጌዴል ልጆች፥

57፤ የሰፋጥያስ ልጆች፥ የሐጢል ልጆች፥ የፈክራት ልጆች፥ የሐፂቦይም ልጆች፥ የአሚ ልጆች።

58፤ እነዚህ ናታኒም ሁሉና የሰሎሞን ባሪያዎች ልጆች ሦስት መቶ ዘጠና ሁለት ነበሩ።

59፤ ከቴልሜላ፥ ከቴላሬሳ፥ ከክሩብ፥ ከአዳን፥ ከኢሜር የወጡ እነዚህ ነበሩ፤ ነገር ግን የአባቶቻቸውን ቤቶችና ዘራቸውን ወይም ከእስራኤል ወገን መሆናቸውን ያስታውቁ ዘንድ አልቻሉም፤

60፤ የዳላያ ልጆች፥ የጦብያ ልጆች፥ የኔቆዳ ልጆች፥ ስድስት መቶ አምሳ ሁለት ነበሩ።

61፤ ከካህናቱም ልጆች፤ የኤብያ ልጆች፥ የአቆስ ልጆች፥ ከገለዓዳዊው ከቤርዜሊ ልጆች ሚስት ያገባ፥ በስሙም የተጠራ የቤርዜሊ ልጆች።

62፤ እነዚህ በትውልድ መጽሐፍ ትውልዳቸውን ፈለጉ፤ ነገር ግን አልተገኘም፥ ከክህነትም ተከለከሉ።

63፤ ሐቴርሰታም። በኡሪምና በቱሚም የሚፈርድ ካህን እስኪነሣ ድረስ ከቅዱሰ ቅዱሳን አትበሉም አላቸው።

64፤65፤ ሰባት ሺህ ሦስት መቶ ሠላሳ ሰባት ከነበሩ ከሎሌዎቻቸውና ከገረዶቻቸው ሌላ ጉባኤው ሁሉ አርባ ሁለት ሺህ ሦስት መቶ ስድሳ ነበሩ። ሁለት መቶም ወንዶችና ሴቶች መዘምራን ነበሩአቸው።

66፤ ፈረሶቻቸውም ሰባት መቶ ሠላሳ ስድስት በቅሎቻቸውም ሁለት መቶ አርባ አምስት፥

67፤ ግመሎቻቸውም አራት መቶ ሠላሳ አምስት፥ አህዮቻቸውም ስድስት ሺህ ሰባት መቶ ሀያ ነበሩ።

68፤ በኢየሩሳሌምም ወዳለው ወደ እግዚአብሔር ቤት በመጡ ጊዜ ከአባቶች ቤቶች አለቆች አያሌዎች ለእግዚአብሔር ቤት በስፍራው ይሠራ ዘንድ በፈቃዳቸው ሰጡ።

69፤ ስድሳ አንድ ሺህም የወርቅ ዳሪክ፥ አምስት ሺህም ምናን ብር፥ አንድ መቶም የካህናት ልብስ እንደ ችሎታቸው ወደ ሥራው ቤተ መዛግብት አቀረቡ።

70፤ ካህናቱና ሌዋውያኑም፥ ከሕዝቡም አያሌዎች፥ መዘምራኑና በረኞቹም፥ ናታኒምም በከተሞቻቸው፥ እስራኤልም ሁሉ በከተሞቻቸው ተቀመጡ።