መዝሙር 121

የመዓርግ መዝሙር።

1 ዓይኖቼ ወደ ተራሮች አነሣሁ፤ ረዳቴ ከወዴት ይምጣ?

2 ረዳቴ ሰማይና ምድርን ከሠራ ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው።

3 እግርህን ለመናወጥ አይሰጠውም፤ የሚጠብቅህም አይተኛም።

4 እነሆ፥ እስራኤልን የሚጠብቅ አይተኛም አያንቀላፋምም።

5 እግዚአብሔር ይጠብቅሃል፥ እግዚአብሔርም በቀኝ እጅህ በኩል ይጋርድሃል።

6 ፀሐይ በቀን አያቃጥልህም ጨረቃም በሌሊት።

7 እግዚአብሔር ከክፉ ሁሉ ይጠብቅሃል፥ ነፍስህንም ይጠብቃታል።

8 ከዛሬ ጀምሮ እስከ ዘላለም እግዚአብሔር መውጣትህና መግባትህን ይጠብቃል።