ምዕራፍ 7።

1፤ እንዲህም ሆነ፤ ቅጥሩ ከተሠራ በኋላ፥ ሳንቃዎቹንም ካቆምሁ በኋላ፥ በረኞቹና መዘምራኑ ሌዋውያኑም ከተሾሙ በኋላ፥

2፤ ወንድሜን አናኒንና የግንቡን አለቃ ሐናንያን በኢየሩሳሌም ላይ ሾምኋቸው፤ እርሱም እውነተኛ ከሌሎቹም ይልቅ እግዚአብሔርን የሚፈራ ሰው ነበረ።

3፤ እኔም። ፀሐይ እስኪሞቅ ድረስ የኢየሩሳሌም በሮች አይከፈቱ፤ እነርሱም ቆመው ሳሉ ደጆቹን ይዝጉ፥ ይቈልፉም፤ ከኢየሩሳሌምም ሰዎች አንዳንዱን በየተራው አንዳንዱንም በየቤቱ አንጻር ጠባቆችን አስቀምጡ አልኋቸው።

4፤ ከተማይቱም ሰፊና ታላቅ ነበረች፤ በውስጥዋ የነበሩ ሕዝብ ግን ጥቂቶች ነበሩ፥ ቤቶቹም አልተሠሩም ነበር።

5፤ አምላኬም ታላቆቹንና ሹማምቱን ሕዝቡንም ሰብስቤ እቈጥራቸው ዘንድ በልቤ አደረገ፤ አስቀድመው የመጡትን ሰዎች የትውልድ መጽሐፋቸውን አገኘሁ፥ በእርሱም እንደዚህ ተጽፎ አገኘሁ።

6፤ የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነፆር ከማረካቸው ምርኮኞች ወደ ኢየሩሳሌምና ወደ ይሁዳ ወደ እየከተማቸው የተመለሱት የአገር ልጆች እነዚህ ናቸው።

7፤ ከዘሩባቤል፥ ከኢያሱ፥ ከነህምያ፥ ከአዛርያስ፥ ከረዓምያ፥ ከነሐማኒ፥ ከመርዶክዮስ፥ ከበላሳን፥ ከሚስጴሬት፥ ከበጉዋይ፥ ከነሑም፥ ከበዓና ጋር መጡ።

8፤ የእስራኤልም ሕዝብ ሰዎች ቍጥር ይህ ነው፤ የፋሮስ ልጆች፥ ሁለት ሺህ መቶ ሰባ ሁለት።

9፤ የሰፋጥያስ ልጆች ሦስት መቶ ሰባ ሁለት።

10፤ የኤራ ልጆች፥ ስድስት መቶ አምሳ ሁለት።

11፤ ከኢያሱና ከኢዮአብ ልጆች የሆኑ የፈሐት ሞዓብ ልጆች፥ ሁለት ሺህ ስምንት መቶ አሥራ ስምንት።

12፤ የኤላም ልጆች፥ ሺህ ሁለት መቶ አምሳ አራት።

13፤ የዛቱዕ ልጆች፥ ስምንት መቶ አርባ አምስት።

14፤ የዘካይ ልጆች፥ ሰባት መቶ ስድሳ።

15፤ የቢንዊ ልጆች፥ ስድስት መቶ አርባ ስምንት።

16፤ የቤባይ ልጆች፥ ስድስት መቶ ሀያ ስምንት።

17፤ የዓዝጋድ ልጆች፥ ሁለት ሺህ ሦስት መቶ ሀያ ሁለት።

18፤ የአዶኒቃም ልጆች፥ ስድስት መቶ ስድሳ ሰባት።

19፤ የበጉዋይ ልጆች፥ ሁለት ሺህ ስድሳ ሰባት።

20፤ የዓዲን ልጆች፥ ስድስት መቶ አምሳ አምስት።

21፤ የሕዝቅያስ ወገን የአጤር ልጆች፥ ዘጠና ስምንት።

22፤ የሐሱም ልጆች፥ ሦስት መቶ ሀያ ስምንት።

23፤ የቤሳይ ልጆች፥ ሦስት መቶ ሀያ አራት።

24፤ የሐሪፍ ልጆች፥ መቶ አሥራ ሁለት።

25፤ የገባዖን ልጆች፥ ዘጠና አምስት።

26፤ የቤተ ልሔምና የነጦፋ ሰዎች፥ መቶ ሰማንያ ስምንት።

27፤ የዓናቶች ሰዎች፥ መቶ ሀያ ስምንት።

28፤ የቤትዓዝሞት ሰዎች፥ አርባ ሁለት።

29፤ የቂርያትይዓሪምና የከፊራ የብኤሮትም ሰዎች፥ ሰባት መቶ አርባ ሦስት።

30፤ የራማና የጌባ ሰዎች፥ ስድስት መቶ ሀያ አንድ።

31፤ የማክማስ ሰዎች፥ መቶ ሀያ ሁለት።

32፤ የቤቴልና የጋይ ሰዎች፥ መቶ ሀያ ሦስት።

33፤ የሁለተኛው ናባው ሰዎች፥ አምሳ ሁለት።

34፤ የሁለተኛው ኤላም ልጆች፥ ሺህ ሁለት መቶ አምሳ አራት።

35፤ የካሪም ልጆች፥ ሦስት መቶ ሀያ።

36፤ የኢያሪኮ ልጆች፥ ሦስት መቶ አርባ አምስት

37፤ የሎድና የሐዲድ የኦኖም ልጆች፥ ሰባት መቶ ሀያ አንድ።

38፤ የሴናዓ ልጆች፥ ሦስት ሺህ ዘጠኝ መቶ ሠላሳ።

39፤ ካህናቱ፤ ከኢያሱ ወገን የዮዳኤ ልጆች፥ ዘጠኝ መቶ ሰባ ሦስት።

40፤ የኢሜር ልጆች፥ ሺህ አምሳ ሁለት።

41፤ የፋስኮር ልጆች፥ ሺህ ሁለት መቶ አርባ ሰባት።

42፤ የካሪም ልጆች፥ ሺህ አሥራ ሰባት።

43፤ ሌዋውያኑ፤ ከሆዳይዋ ወገን የኢያሱና የቀድምኤል ልጆች፥ ሰባ አራት።

44፤ መዘምራኑ፤ የአሳፍ ልጆች፥ መቶ አርባ ስምንት።

45፤ በረኞቹ፤ የሰሎም ልጆች፥ የአጤር ልጆች፥ የጤልሞን ልጆች፥ የዓቁብ ልጆች፥ የሐጢጣ ልጆች፥ የሶባይ ልጆች፥ መቶ ሠላሳ ስምንት።

46፤ ናታኒም፥ የሲሐ ልጆች፥ የሐሡፋ ልጆች፥

47፤ የጠብዖት ልጆች፥ የኬራስ ልጆች፥ የሲዓ ልጆች፥

48፤ የፋዶን ልጆች፥ የልባና ልጆች፥

49፤ የአጋባ ልጆች፥ የሰምላይ ልጆች፥ የሐናን ልጆች፥ የጌዴል ልጆች፥ የጋሐር ልጆች፥

50፤ የራያ ልጆች፥ የረአሶን ልጆች፥ የኔቆዳ ልጆች፥

51፤ የጋሴም ልጆች፥ የዖዛ ልጆች፥ የፋሴሐ ልጆች፥

52፤ የቤሳይ ልጆች፥ የምዑናውያን ልጆች፥

53፤ የንፉሰሲም ልጆች፥ የበቅቡቅ ልጆች፥ የሐቀፋ ልጆች፥ የሐርሑር ልጆች፥

54፤ የበስሎት ልጆች፥ የምሒዳ ልጆች፥ የሐርሻ ልጆች፥

55፤ የበርቆስ ልጆች፥ የሲሣራ ልጆች፥

56፤ የቴማ ልጆች፥ የንስያ ልጆች፥ የሐጢፋ ልጆች።

57፤ የሰሎሞን ባሪያዎች ልጆች፤ የሶጣይ ልጆች፥ የሶፌሬት ልጆች፥ የፍሩዳ ልጆች፥

58፤ የየዕላ ልጆች፥ የደርቆን ልጆች፥ የጌዴል ልጆች፥

59፤ የሰፋጥያስ ልጆች፥ የሐጢል ልጆች፥ የፈከራት ልጆች፥ የሐፂቦይም ልጆች፥ የአሞን ልጆች።

60፤ ናታኒም ሁሉና የሰሎሞን ባሪያዎች ልጆች ሦስት መቶ ዘጠና ሁለት ነበሩ።

61፤ ከቴልሜላ፥ ከቴላሬሳ፥ ከክሩብ፥ ከአዳን፥ ከኢሜር የወጡ እነዚህ ናቸው፤ ነገር ግን የአባቶቻቸውን ቤቶችና ዘራቸውን ወይም ከእስራኤል ወገን መሆናቸውን ያስታውቁ ዘንድ አልቻሉም፤

62፤ የዳላያ ልጆች፥ የጦብያ ልጆች፥ የኔቆዳ ልጆች፥ ስድስት መቶ አርባ ሁለት።

63፤ ከካህናቱም የኤብያ ልጆች፥ የአቆስ ልጆች፥ ከገለዓዳዊው ከቤርዜሊ ልጆች ሚስት ያገባ በስሙም የተጠራ የቤርዜሊ ልጆች።

64፤ እነዚህ በትውልድ መጽሐፍ ትውልዳቸውን ፈለጉ፥ ነገር ግን አልተገኘም፤ ከክህነትም ተከለከሉ።

65፤ ሐቴርሰታም። በኡሪምና በቱሚም የሚፈርድ ካህን እስኪነሣ ደረስ ከተቀደሰው ነገር አትበሉም አላቸው።

66፤67፤ ሰባት ሺህ ሦስት መቶ ሠላሳ ሰባት ከነበሩ ከሎሌዎቻቸውና ከገረዶቻቸው ሌላ ጉባኤው ሁሉ አርባ ሁለት ሺህ ሦስት መቶ ስድሳ ነበሩ፤ ሁለቱ መቶም አርባ አምስት ወንዶችና ሴቶች መዘምራን ነበሩአቸው።

68፤ ፈረሶቻቸውም ሰባት መቶ ሠላሳ ስድስት፥ በቅሎቻቸውም ሁለት መቶ አርባ አምስት፥

69፤ ግመሎቻቸውም አራት መቶ ሠላሳ አምስት፥ አህዮቻቸውም ስድስት ሺህ ሰባት መቶ ሀያ ነበሩ።

70፤ ከአባቶች ቤቶች አለቆችም አያሌዎቹ ሰዎች ስለ ሥራው ስጦታ ሰጡ። ሐቴርሰታም አንድ ሺህ የወርቅ ዳሪክ፥ አምሳም ድስቶች፥ አምስት መቶ ሠላሳም የካህናት ልብስ በቤተ መዛግብት ውስጥ ሰጠ።

71፤ ከአባቶች ቤቶች አለቆችም አያሌዎቹ በሥራው ቤተ መዛግብት ውስጥ ሀያ ሺህ የወርቅ ዳሪክ፥ ሁለት ሺህ ሁለት መቶም ምናን ብር ሰጡ።

72፤ የቀሩትም ሕዝብ የሰጡት ሀያ ሺህ የወርቅ ዳሪክና ሁለት ሺህ ምናን ብር፥ ስድሳ ሰባትም የካህናት ልብስ ነበረ።

73፤ ካህናቱና ሌዋውያኑም፥ በረኞቹና መዘምራኑም ከሕዝቡም አያሌዎቹ፥ ናታኒምም፥ እስራኤልም ሁሉ በከተሞቻቸው ተቀመጡ።